የማን ሲቲው ሜንዲ አሳዛኙ ኮከብ..

ቤንጃሚን ሜንዲ ለፕሪምየር ሊግ ክለብ ማንቸስተር ሲቲ እና ለፈረንሳይ ብሄራዊ ቡድን በግራ ተከላካይነት የሚጫወት ፈረንሳዊ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋች ነው። ለማርሴይ በ2016 Coupe de la Ligue እንዲያሸንፍ ረድቶታል።በ2017 በ52 ፓውንድ ማንቸስተር ሲቲን ተቀላቅሏል ይህም በወቅቱ በዓለም እግር ኳስ ውዱ ተከላካይ እንዲሆን አድርጎታል። ከማንቸስተር ሲቲ ጋር የፕሪምየር ሊግ እና የኤፍኤ ካፕ ዋንጫን አንስቷል። በአለም አቀፍ ደረጃ ፈረንሳይን በመወከልም የ2018 የፊፋ የአለም ዋንጫን ያሸነፈው ቡድን አካል ነበር።

አርሰናል በቻፒየንስ
ሊግ ድል ሲቀናው ግብ ጠባቂው ዴቪድ ራያ ደምቆ አምሽቶል

በ2018 ዴቪድ ራያ በEFL ሊግ 1 ለብላክበርን ሮቨርስ እየተጫወተ ነበር።

በ 2024 አሁን ከአርሰናል ጋር በፕሪሚየር ሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል እና በፖርቶ ላይ 2 ፍፁም ቅጣት ምቶችን በማዳን ከ 14 ዓመታት በኋላ በቻምፒየንስ ሊግ ለመጀመሪያ ጊዜ ቡድኑን ወደ ሩብ ፍፃሜ አሳልፏል።

አርሰናል 1 0 ፖርቶ

በፍጽም ቅጣት ምት አርሰናል አሸናፊ ሆኖል 

ታማኙ ግብ ጠባቂ አልታመነም። 

ዴቪድ ዴ ሂያ የስፔን ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋች ሲሆን ለፕሪምየር ሊግ ክለብ ማንቸስተር ዩናይትድ እና ለስፔን ብሄራዊ ቡድን በረኛ ሆኖ ተጫውቶል። በአለም ላይ ካሉ ምርጥ ግብ ጠባቂዎች አንዱ ተደርጎ ይጠቀሳል። በመጨረሻም ታማኙ ግብ ጠባቂ በቴናግ አልታመነም። የሚገባውን የክብር ሽኝት አላደረገም። 

 የማንችስተር ዩናይትድ 3ኛ መለያን እንዴት አገኛችኹት?

Sports Wave

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከረጅም በረራ በኋላ አዲስ አበባ ደርሷል።                                                                          EFF

3.jpg

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአሜሪካ ቆይታን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሐሙስ ነሐሴ 4/2015 ከቀኑ 9፡00 በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተዘጋጅቷል። ኢእፌ

ሃሪኬን የስፐርሱ ምርጥ ጎል አዳኝ
ቶተንሃም  ከ200 በላይ ጎሎችን ለእንግሊዝ ደግሞ  ከ50 በላይ ጎሎችን አስቆጥሯል። ሁለት ጊዜ የኢኤፍኤል ዋንጫ አሸንፍል። 
ኢልካይ ጉንዶጋን በ2016 ከቦሩሲያ - ዶርትመንድ ማን-ሲቲን ተቀላቀለ። ከሲቲ ጋር ፕሪሚየርሊግየኤፍኤካፕየኢኤፍኤልየአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አንስቷል። 
ዣካ  በ FC Basel  ሁለት የሊግ ንጫዎችን እና የስዊስ ዋንጫን አሸንፏል።
በ2016 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለብን ተቀላቅሎ በ2019 የክለቡ ካፒቴን በመሆን የአመራር ብቃቱን አሳይቷል።
10 በተቃራኒ ደጋፊዎች  የሚወደዱ  ተጫዎቾች
9 አባት እና ልጅ በተመሳሳዪ ክለብ 

ክብረቢስ የማንቸስተር አመራሮች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአትላንታ በሚያከናውነው ጨዋታ ምትክ ሌላ የወዳጅነት ጨዋታ ያደርጋል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ በማምራት ባሳለፍነው ረቡዕ ከጉያና ጋር የወዳጅነት ጨዋታ አድርጎ 2-0 ማሸነፉ የሚታወስ ሲሆን በቀጣይ ቅዳሜ ከአትላንታ ሮቨርስ ጋር ሁለተኛ ጨዋታ ለማድረግ ቀጠሮ ቢይዝም አዘጋጁ ተቋም የጨዋታው ትኬት በበቂ ሁኔታ እንዳልተሸጠ በመግለፅ ጨዋታው እንዲሰረዝ መጠየቀን ተከትሎ በአትላንታው ጨዋታ ምትክ ሌላ የወዳጅነት ጨዋታ እንዲዘጋጅ ተደርጓል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አትላንታ የማይጓዝ ሲሆን በምትኩ በዋሺንግተን ዲሲ ቆይታ በማድረግ የተለያዩ ጨዋታዎች ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ይገኛል። በዚህም መሰረት በመጪው ቅዳሜ ሐምሌ 29 ከሎዶን ዩናይትድ ጋር በሴግራ ፊልድ የሚጫወት ይሆናል። ሎዶን ዩናይትድ መቀመጫውን በሊዝበርግ ቨርጂንያ ያደረገና በUCL Championsip የሚካፍል ቡድን ሲሆን ብሔራዊ ቡድናችን ከጉያና ጋር ያደረገው ጨዋታ የተካሄደበት ሴግራ ፊልድ ባለንብረት ነው።

ከቅዳሜው የወዳጅነት ጨዋታ በመቀጠል ብሔራዊ ቡድናችን ከዲሲ ዩናይትድ ክለብ ጋር ጨዋታ እንዲያደርግ የተለያዩ ጥረቶች በመደረግ ላይ የሚገኙ ሲሆን ክለቡ ይህን ጨዋታ እንዲያደርግ በአሜሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (US SOCCER) ፍቃድ ካገኘ የሚካሄድ ይሆናል። ለዚህም ጨዋታ መሳካት የዲሲ ዩናይትድ ክለብ ባለድርሻ የሆኑት ኢዮብ ማሞ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ የሚገኙ ሲሆን ለዚህ እና በአጠቃላይ ቡድናችን በአሜሪካ ቆይታው ላይ እያደረጉት ለሚገኘው ትብብር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ልባዊ ምስጋውን ያቀርባል።

 ኢእፌ

Live Score